AM/Prabhupada 0150 - መዘመርን ማቆም አይገባንም፡

The printable version is no longer supported and may have rendering errors. Please update your browser bookmarks and please use the default browser print function instead.


Lecture on SB 6.1.15 -- Denver, June 28, 1975

“አትሃፒ ቴ ዴቫ ፓዳምፑጃ ድቫያም ፕራሳዳ ሌሻኑግርሂታ ኤቫ ሂ ጃናቲ ታትቫም ና ቻንያ ኤኮ ፒ ቪቺቫን” (ሽብ 10 14 29) እነዚያ በክርሽና በረከት የተመረቁ:ክርሽናን ለማወቅ ይችላሉ: ሌሎች ግን:“ና ቻንያ ኤኮ ፒ ቺራም ቪቺንቫን” ቺራም ማለት ለረጅም ግዜ ማለት ነው:ክርሽና ማን እንደሆነ ግምት ውስጥ ቢገቡ ብዙ አመትም አይበቃቸውም: ይህም ክርሽናን ለመረዳት ነው:የግምት ሂደት አይጠቅመንም: እንደዚህም ብዙ የቬዲክ ጥቅሶች አሉ: “አታህ ሽሪ ክርሽና ናማዲ ና ብሃቬድ ግራሃያም ኢንድሪያኒ ሴቮን ሙክሄ ሂ ጂቫዶ ስቫያም ኤቫ ስፑራትሂ አዳሃ” :(ቼቻ ማድህያ 17 136) ክርሽና:ስሙ:ዝናው:አንደበቱ:ስራው: “ሽሪ ክርሽና ናማዲ ና ብሃቬድ” ናማዲ ማለት:“ከቅዱስ ስሙ ጀምሮ ማለት ነው” ምንድን ነው የማይቻለው?“እራሳችንን በአለማዊ መድረክ ካስቀመጥን” ለአንድ ሺህ አመት ያህልም ብንዘምር:ለመራመድ አስቸጋሪ ይሆናል:ይህም “ናማ አፐራድ” ይባላል: ቢሆንም ግን:ቅዱስ ስም ሃይል ስለ አለው:በመዘመር ብቻ:ቀስ በቀስ አንድ ሰው ንጹህ ሊሆን ይችላል: ስለዚህም መዘመርን ማቆም የለብንም:በተገኘንበት ሁኔታ:ሀሬ ክርሽና መዘመር አለብን: ነገር ግን እራሳችንን በአለማዊ መድረክ ላይ ካስቀመጥን:ክርሽናን ሙሉ በሙሉ ለማወቅ እና መረዳት ያዳግተናል: ቅዱስ ስሙን:አንደበቱን:ፎርሙን:ስራውን:መረዳት አዳጋች ይሆናል: ለዚህም ስርአቱ ብሃክቲ ነው: ክርሽናን ደግሞ ለመራዳት ስትበቁ: ወዲያውኑ ወደ መንፈሳዊ አለም ለመሄድ:ብቁ ትሆናላችሁ: ክርሽናም ይህንን በብሃገቨድ ጊታ ጠቅሶታል: “ትያክትቫ ዴሀም ፑናር ጃንማ ናይቲ ማም ኢቲ”(ብጊ 4 9).