AM/Prabhupada 0016 - መስራት እፈልጋለሁ፡፡



Lecture on BG 7.1 -- San Francisco, March 17, 1968

እንዴት ከጌታ ክርሽና ጋር መገናኘት እንደምንችል ማወቅ አለብን: ክርሽና ሁሉም ቦታ ላይ ይገኛል: ይህ የክርሽና ንቃተ ማህበር እንቅስቃሴ ነው: ይህ የክርሽና ንቃት ነው: እንዴት ከተለያዩ ፎርሞች ክርሽናን እንደምናገኝ ማወቅ አለብን: ከእንጨትም ሆነ: ከብረት: ከተገኘው ነገር: ክርሽና ከሁሉም ቦታ ይገኛል: እንዴት በሁሉም ነገር ከክርሽና ጋር መገናኘት እንደምንችል መማር አለብን: ይህ በዚህ ዮጋ ሲስተም ተገልጧል እና መማር ትችላላችሁ: የክርሽና ንቃትም ዮጋ ነው: ትክክለኛው ዮጋ: ከዮጋዎች ሁሉ በከፍተኛ ደረጃ የሚታየው ዮጋ ነው: ማንም ዮጊ ቢመጣ ይህንን ለማሳመን እንችላለን: ይህም የዮጋ 1ኛ ዮጋ ሲስተም ነው ማለት እንችላለን: ይህ 1ኛ ነው:ሁኖም ለመለማመድም በጣም ቀላል ነው: ገላችሁን ማለማመድ አያስፈልጋችሁም: ለምሳሌ አቅመ ደካማ ልትሆኑ ትችላላችሁ: ለክርሽና ንቃት ግን: ምንም ድካም አይሰማችሁም: የእኛ ተማሪዎች በክርሽና ንቃተ ማህበር እንቅስቃሴ ስራ:በጣም አገልግሎቱ እንዲበዛላቸው ነው ምኞታቸው: “ስዋሚጂ ምን ላድርግ? ምን ልስራ?” ብለው ሁሌ እንደጠየቁ ነው: በጣም ጥሩም ስራ እየሰሩ ይገኛሉ: ድካምም አይሰማቸውም: ይህ የክርሽና ንቃት ነው: በዚህ ምድራዊ አለም ከስራ በኋላ ድካም ይመጣል: እረፍትም ያስፈልጋል: ይህንንም ስል እየአጋነንኩት አይደለም: እኔ የ72 አመት እድሜዬ የገፋ ሰው ነኝ: አንድ ግዜም ታምሜ ወደ ሕንድ ሂጄ ነበረ: ነገር ግን ተመልሼ መጥቻለሁ: ለማገልገልም እሻለሁ: ለመስራት እፈልጋለሁ: ከዚህ ሁሉ ስራ ተርፌ: ጡረተኛ ሁኜ: መቀመጥ እችል ነበር: ነገር ግን ምኞቴ ለማገልገል ነው: እስከቻልኩኝ ድረስ: ለማገልገል እሻለሁ: ቀን እና ሌሊት ማገልገል እሻለሁ:ማታ ማታ በዲክታ ፎን እየተጠቀምኩ እሰራለሁ: ካልሰራሁኝም ቅር ይለኛል: ይህ የክርሽና ንቃት ነው: ለማገልገል ሁላችን በጣም ፍላጎት እንዲኖረን ያስፈልጋል: ይህ እንቅስቃሴ የሌለው ህብረተሰብ አይደለም: የሚበቃ ስራ በእጃችን አለ: ወረቀቶችን ማረም: ማተም:እና የመሽጥም ስራ አለ: እንዲሁም የክርሽና ንቃት እንዴት እንደሚስፋፋም ጥታት አድርጉ: ይህ የተግባራዊ የክራሽና ንቃት ስራ ነው: