AM/Prabhupada 0080 - ክርሽና ከልጅ ጓደኞቹ ጋር መጫወትን በጣም ይወዳል፡፡



Lecture on CC Madhya-lila 21.13-49 -- New York, January 4, 1967

"ኤ ማታ አንያትራ ናሂ ሹኒዬ አድብሁታ ያሀራ ሽራቫኔ ቺታ ሃያ አቫድሁታ" "ክርሽና ቫትሴይር አሳንክህያቴያህ ሹካዴቫ ቫኒ ክርሽና ሳንጌ ካታ ጎፓ ሳንክህያ ናሂ ጃኒ (ቼቻ ማድህያ 21.18-19) ጐፓ ክርሽና እንደምታውቁት በመኖርያው ሰፍራ እያለ ልክ እንደ 16 ዓመት ልጅ ይመሰል ነበር፡፡ ዋነኛው እንቅስቃሴውም ላሞችን ከጓደኞቹ እና ከእረኞቹ ጋር ሆኖ ወደ ግጦሽ መሬት ማሰማራት ነበረ፡፡ በዚህም መልክ ግዜውን በደስታ ማሳላፍ ነው፡፡ የክርሽናም የቀን በቀን እንቅስቃሴ ይህን ይመስላል፡፡ ሰለዚህም ሱካዴቭ ጎስዋሚ አንድ ቆንጆ ጥቅስ ፅፎ ይገኛል። ይህም እነዚህ ከክርሽና ጋር የሚጫወቱት ልጆች በሕይወታቸው ብዙ በረከት የሞላበትን እንቅስቃሴ በማድረግ ፃድቅነትን ያከማቹ ነበሩ፡፡ ክርታ ፑንያ ፑንጃሀ (ሽብ 10.12.11) ሳካም ቪጃህሩህ ኢትሀም ሳታም ብራህማ ሱክሀኑብሁትያ ሱካዴቭ ጎስዋሚ እንደፃፈውም እነዚህ ከክርሽና ጋር የሚጫወቱት ልጆች እነማን ናቸው? የሚጫወቱትም ፍፁም እውነት ከሆነው አብዩ ጌታ ጋር ነው፡፡ ይህም አብይ ጌታ ሰብዓዊነት እንደሌለው በአንዳንድ ታላላቅ ባህታውያን ይገመት የነበረው ነው፡፡ “ኢታም ሳታም ብራህማ” ብራህማ ሱክሀ፡፡ ብራህማ ወይንም የተወሰነ ደረጃ ያለው መንፈሳዊ ንቃት ያላቸው ማለት ነው፡፡ ይህም የብራህማን ንቃት ኩሬ አብዩ ሽሪ ክርሽና እዚህ ነበረ፡፡ እነዚህም ከክርሽና ጋር ይጫወቱ የነበሩት ልጆች እርሱም የብራህማን ንቃት ሁሉ ኩሬ ነው፡፡ ኢትሀም ሳታም ብራህማ ሱክሃኑብሁትያ ዳስያም ጋታናም ፓራ ዳይቫቴና ዳሽያም ጋታናም ማለት ዓብዩ ጌታን እንደ ጌታቸው የተቀበሉ ትሁት አገልጋዮች ማለት ነው፡፡ ለእነርሱም ይህ ክርሽና አብዩ ጌታ ሰለመሆኑ ጥርጥር የለውም፡፡ በጌታ ሰብአዊነት ለማያምኑ ክርሽና አብዩ ብራህማን ወይም ነፍስ ሲሆን ለትሁት አገልጋዮቹ ደግሞ አብዩ ጌታ ሆኖ ይገኛል፡፡ “ማያሽሪታናም ናራ ዳራኬና” በቁሳዊው ዓለም ሕይወት ሰመመን ውስጥ ለሚገኙት ደግሞ ክርሽና ልክ እንደ ተራ ልጅ ሆኖ ይታያቸዋል፡፡ ማያሽቲታናም ናራ ዳራኬና ሳካም ቪሃህሩህ ክርታ ፑንያ ፑንጃሀ (ሽብ 10.12.11) ከእርሱም ጋር በሚሊዮን በሚቆጠረው ትውልዳቸው እና ህይወታቸው ብዙ በረከትን እና መንፈሳዊ ፀጋን ያከማቹ ልጆች ይገኛሉ፡፡ ይህም መንፈሳዊ ፀጋ ከክርሽና ጋር ፊት ለፊት በመሆን እና ልክ እንደ ማናቸውም ልጆች ሆነው እንዲጫወቱ አበቃቸው፡፡ እንደእነሱም ክርሽና ፍቅር ከተሞላባቸው ልጆች ጋር መጫወትን ይወዳል፡፡ ይህም በብራህማ ሰሚታ ውስጥ ተጠቅሷል። ሱራብሂ አብሂፓላያንታም ላክሽሚ ሳሀስራ ሻታ ሳምብህራማ ሴቭያማናም (ብሰ 5 29) እነዚህም እንቅስቃሴዎች ሁሉ በእነዚህ ጥቅሶች ውስጥ ተጠቅሰዋል፡፡ ኤካ ኤካ ጎፓ ካሬ ዬ ቫትሳ ቻራና ኮቲ አርቡዳ ሻንክሀ ፓድማ ታሀራ ጋናና (ቼቻ ማድህያ 21.20) ለመቁጠር የሚያዳግት ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ጓደኞች እና እረኞች ይገኙ ነበር፡፡ ሁሉም ለመቁጠር የሚያዳግት ነበረ፡፡ ለመቁጠር የሚያዳግቱ ላሞች ጓደኞች ነበሩ፡፡ ቬትራ ቬኑ ዳላ ሽርንጋ ቫስትራ አላንካራ ጎፓ ጋኔራ ያታ ታራ ናሂ ሌክሀ ፓራ (ቼቻ ማድህያ 21.21) እነዚህም እረኞች በእጃቸው ”ቬትራ“ ወይም የእረኛ ዱላ ይዘው ይገኙ ነበረ፡፡ እንደዚሁም ሁሉ እያንዳንዳቸው ዋሽንትም ይዘው ይገኙ ነበረ፡፡ ”ቬትራ ቬኑ ዳላ“ እንደዚሁም የሎተስ አበባ የቀንድ ጡሩንባ እና ”ሽርንጋራ“ ይዘው ይገኙ ነበር፡፡ ሽርንጋራ ቫስትራ ቆንጆ በሆነ መንገድም ለልብሰው እና በጌጣጌጥም አሸብረቀው ይገኙ ነበረ፡፡ ልክ ክርሽና አሸብርቆ ይገኝ እንደነበረም ሁሉ ጓደኞቹም አሸብርቀው ይገኙ ነበረ፡፡ ወደ መንፈሳዊ ዓለምም ስትሄዱ ማን ክርሽና እንደሆነ እና ማን ክርሽና እንዳልሆነ ለመለየት ያዳግታል፡፡ ምክንያቱም አብዩ ጌታ በሰጠው ፀጋ ሁሉም ፍጡር እንደ ክርሽና በመሆኑ ነው፡፡ በቫይኩንታ መንፈሳዊ ፕላኔቶችም ሁሉም ቪሽኑን ተመስለው ይገኛሉ፡፡ ይህም “ሳሩፕያ ሙክቲ” ተብሎ ይታወቃል፡፡ እነዚህም ነፍሳት ወደ መንፈሳዊው ዓለም ሲመለሱ ልክ እንደ ክርሽና ወይንም እንደ ቪሽኑ ተመስለው ይገኛሉ፡፡ በመሀከላቸውም ምንም ልዩነት ያለ አይመስልም፡፡ ምክንያቱም ይህ መንፈሳዊ ዓለም ፍፁም በመሆኑ ነው፡፡ እዚህም ዓለም ላይ ግን ልዩነቱ ሊታይ ይችላል፡፡ እነዚህም በአብዩ አምላክ ሰብአዊነት የማያምኑ ምንም እንኳን ግል ሰብአዊነት ቢኖርም የሰብዓዊ አንድነትም እንዳለ ለማወቅ ያዳግታቸዋል፡፡ የግል ሰብዓዊነትም ሲያስቡ ወዲያውኑ ልዩነት አለ ብለው ያስባሉ፡፡ ይህ ከሆነማ ነፃነት የምንለው ምኑ ላይ ነው፡፡ በእርግጥ በመንፈሳዊ ዓለም ላይ ምንም ልዩነት የለም፡፡ ያለው ልዩነት ግን የክርሽና አንደበት እና የሌሎቹ ሁሉ አንደበት ነው፡፡ እነርሱም “ክርሽና የፍቅራችን ሁሉ መድረሻ ነው” ብለው ያመኑ ናቸው፡፡ በመሀከል የሚገኘውም ክርሽና ነው፡፡ በዚህም መንገድ እያንዳንዳቸው ልጆች ልጃገረዶች እና ክርሽና ሁሉም በመንፈሳዊ ደስታ ላይ ይገኛሉ፡፡