AM/Prabhupada 0099 - እንዴት በክርሽና ለመታወቅ እንደምትችሉ፡፡

The printable version is no longer supported and may have rendering errors. Please update your browser bookmarks and please use the default browser print function instead.


Lecture on BG 13.4 -- Bombay, September 27, 1973

በዚህ አለም ላይ የተለያየ ደረጃ ያላቸው ሰዎች አሉ:ምንም እንኳን ብዙዎቹ እንድ ሙምባይ አይነት ወይንም ሌላ ከተማ ውስጥ ቢኖሩም: እንደዚሁም ሁሉ: ሁሉም ነዋሪ ፍጥረታት በአንድ አይነት ደረጃ: የሚገኙ አይደሉም: አንዳንዶቹ “በአለማዊ ጥሩ ባህርይ” የተመሰጡ ናቸው (በጎ አድራጎት): አንዳንዶቹ ደግም “በአለማዊ የቅብዝብዝነት ባህርይ” የተመሰጡ ናቸው አንዳንዶቹ ደግሞ “በአለማዊ የድንቁርና ባህርይ” የተመሰጡ ናቸው: እነዚህም በድርቁርና ባህርይ የተመሰጡ:ልክ ውሃ ውስጥ እንደወደቁ: የእሳት ፍንጣቂዎች ናቸው: የእሳት ፍንጣቂ ልክ ውሀ ላይ እንደወደቀ:እራሱ ወዲያውኑ ይጠፋል: የደረቀው ሳር ላይ ደግሞ:ይኅው የእሳት ፍንጣቂ ቢወድቅበት:የደረቀውን ሳር ተጠቅሞ: እሳት ይለኮስ እና እንደ ገና እሳት ይሆናል: እንደዚሁም ሁሉ:በጥሩ ባህርይ አንደበት የሚገኙ ሰዎች:የክርሽና ንቃታቸውን በቀላሉ ሊቀሰቅሱት ይችላሉ: ምክንያቱም በብሃገቨድ ጊታ እንዲህ ብሎ ተጠቅሷል:“ዬሻም ትቭ አንታ ጋታም ፓፓም” ለምንድን ነው ብዙ ሰዎች ወደ ቤተ መቅደስ የማይሄዱት? ምክንያቱም አንዳንዱ ሰው ባልታረመ ድንቁርና ውስጥ ስለሚገኝ ነው: “ናማም ዱስክሪቲኖ ሙድሃህ ፕራፓድያንቴ ናራድሃማህ (ብጊ7 15) እነዚህም ለመምጣት ፍላጎቱ የላቸውም:በሃጥያታዊ ስራዎች የተሰማሩ ሰዎች:የክርሽናን ንቃት ሊያወድሱ አይችሉም: ይህ የማይሆን ነው:ነገር ግን እድሉ ለሁሉም ተሰጥቷል: እኛም እያቆላመጥናቸው እንገኛለን ”እባክህ ና:እባካችሁ“ ክርሽናን ወክለን የምንሰራው ስራ ይህ ይሆናል ማለት ነው: ልክ ክርሽና እዚህ አለም ላይ ብሃገቨድ ጊታን ለማስተማር: መጥቶ እንደጠየቀን ሁሉ: ”ሳርቫ ድሃርማን ፓሪትያጃ ማም ኤካም ሻራናም ቭራጃ“ (ብጊ18 66)(ሙሉ ልቦናህን ስጠኝ) ክርሽናም ይህንን በጣም ያመሰግነዋል ”እነዚህ አገልጋዮች በእኔ ተወካይነት እያስተማሩ ነው“ ”እዚያ ለማስተማር ባልሄድም:እነርሱ ስራዬን እየሰሩልኝ ነው:“ ምን አይነት ስራ ላይ ነው የተሰማራነው?ሰዎችን ”እባካችሁ ለክርሽና ልቦናችሁን ስጡ“:ብቻ ነው የምንለው: ስለዚህም ለክርሽና ተወዳጅ ሁነን እንገኛለን:ክርሽናም እንዲህ ብሏል:”ናቻ ታስማን ማኑስዬሱ ካሽቺን ሜ ፕሪያ ክርታማህ (ብጊ18 69) ስራችን ሁሉ እንዴት በክርሽና ታዋቂነትን እንደምናገኝ ነው: አንድ ሰው ወደ ክርሽና ንቃትም ተመለሰ ወይንም አለተመለሰም ግድ አይሰጠንም: ስራችን ማቆላመጥ ነው:ይኅው ነው:“የእኔ ጌታ:እባክህ ወደ እዚህ ና:የክርሽናንም ደይቲ ቀረብ ብለህ እየው” “ስገድለትም እና የሚበላ ፕራሳድም: ቤት ከመሄድህ በፊት ውሰድ” ነገር ግን አንዳንድ ሰዎች እሺ አይሉም:ለምን? ይህ ሰራ በሃጥያት ባህርይ በሞላባቸው ሰዎች ሊወሰድ አይችልም: ስለዚህም ክርሽና እንደዚህ ብሏል:“ዬሻም ትቭ አንታ ጋታም ፓፓም” ከሀጥያቱ ነፃ የሆነ ሰው: “ዬሻም ትቭ አንታ ጋታም ፓፓም ጃናናም ፑንያ ካርማናም” ማነው ከሀጥያት ነፃ ሊሆን የሚችለው?እርሱም በመንፈሳዊ ግልጋሎት ውስጥ የሚገኘው ሰው ነው: በመንፈሳዊ አገልግሎት ሁሌ የተሳተፈ:እንዴት ወደ ሃጥያተኛ መንገድ ሊወድቅ ይችላል? ስለዚህም ዋናው የመንፈሳዊ ስራችን የሃሬ ክርሽናን ቅዱስ ስም ሁል ግዜ መዘመር ነው: ሁል ግዜ ቅዱስ ስሙን ከዘመራችሁ:”ሃሬ ክርሽና:ሃሬ ክርሽና:ክርሽና ክርሽና “ እንደዚሁም በክርሽና ንቃት አእምሮዋችሁ ሁሌ ከተሞላ: በዚህ ሁኔታ:ሌላ የተበከለ አስተሳሰብ ወደ አእምሮዋችሁ ሊገባ አየችልም:ይህ ነው የክርሽና ንቃት ሥርአቱ: ክርሽናን ልክ እንደረሳነውም ግን:የማያ ወጥመድ ወዲያውኑ ትይዘናለች: