AM/Prabhupada 1078 - ሀሳባችን እና አእምሮዋችን 24 ሰዓት ሙሉ በዓብዩ የመላእክት ጌታ መንፈስ የተመሰጠ ቢሆን



660219-20 - Lecture BG Introduction - New York

ወይንም ደግሞ ለዓብዩ የመላእክት ጌታ ጥልቅ የሆነ የፍቅር መንፈስ ቢኖረን ምንም ዓይነቱን ስራ እየሰራን ቢሆንም ዓብዩ ጌታን ሁሌ ለማስታወስ እንችላለን፡፡ ስለዚህ ይህን መንፈሳዊ ፍቅር መቀስቀስ ይኖርብናል፡፡ ይህም ልክ አርጁናም በጦር ሜዳ ላይ እያለ ዓብዩ ጌታን ያስታውስ እንደነበረ ማለት ነው፡፡ አርጁና ከ24 ሰዓት ውስጥ ለአንድ ሰኮንድ እንኳን የሚሆን ግዜ ሽሪ ክርሽናን ዘንግቶ አያውቅም፡፡ አርጁና የሽሪ ክርሽና የቅርብ ጓደኛው እና የጦር ሜዳም ተዋጊ ነበረ፡፡ ዓብዩ ሽሪ ክርሽና ለአርጁና በጦርነቱ ላይ እንዳይዋጋ አልመከረውም፡፡ ወይንም ደግሞ ወደ ጫካ ወ ወደ እንዲሁም ወደ ሂማላያ ተራሮች ለፀሎት እንዲሄድ አልመከረውም፡፡ የቀድሞውንም የዮጋ ስርዓት እንዲከተል ምክር ሲሰጠውም አርጁና ይህንን ስርዓት መከተል እንደማይችል ተናግሮ ነበር፡፡ "ይህንን ስርዓት እኔ ልከተለው አልችልም፡፡" ከዚያም ዓብዩ ጌታ እንዲህ አለ "ዮጊናም አፒ ሳርቬሻም ማድ ጋቴናንታራትማና" (ብጊ፡ 6.47) "ማድ ጋቴናንታራትማና ሽራድሀቫን ብሀጃቴ ዮ ማም ሳ ሜ ዩክታታሞ ማታሀ" እንደተጠቀሰውም አንስ ሰው ዓብዩ የመላእክት ጌታን ሁልግዜ የሚያስታውስ ከሆነ እርሱ ከዮጊዎች ሁሉ በላይ እንደሆነ የታወቀ ነው፡፡ እርሱ ከ "ግያኒዎች" በላይም እንደሆነ የታወቀ ነው፡፡ በተጨማሪም እርሱ ከዓብዩ ጌታ አገልጋዮች ሁሉ የበላይ ነው፡፡ ዓብዩ ጌታ እንዲህ ዓይነት ምክር ሰጥቷል "ታስማት ሳርቬሹ ካሌሹ ማም አኑስማራ ዩድህያ ቻ" (ብጊ፡ 8.7) "ሻታርያ" ወይንም ተዋጊ እስከሆንክ ድረስ ይህን የውጊያ ሀላፊነትህን መወጣት ግዳጅህ ነው፡፡ መዋጋት ይኖርብሀል፡፡" ውጊያም ላይ እያለህ ሁሌ እኔን ለማስታወስ ጥረት ማድረግ ይገባሀል፡፡ በዚህ ልምድ እኔን ሁሌ ለማስታወስ ትችላለህ፡፡ "አንታ ካሌ ቻ ማም ኤቫ ስማራን (ብጊ፡ 8.5) "ይህንን ልምድ በማድረግ በሞት አፋፍ ላይ እያለህ እኔን በቀላሉ ለማስታወስ ትችላለህ፡፡" "ማዪ አርፒታ ማኖ ቡድሂር ማም ኤቫይስያሲ አሳምሻያህ" ይህንንም በመድገም ይህ ጥርጥር የለውም ብሎ ገለፀለት፡፡ አንድ ሰው ሙሉ ልቦናውን ለዓብዩ የመላእክት ጌታ ካቀረበ ይህም እራሱን በመንፈሳዊ የዓብዩ ጌታ የፍቅር አገልግሎት ላይ ካሰማራ "ማዪ አርፒታ ማኖ ቡድሂር" (ብጊ፡ 8.7) ምክንያቱም የምንሰራው በገላችን ብቻ ሳይሆን በሀሳብ እና በአእምሮዋችንም ጭምር ነው፡፡ ስለዚህ ሀሳባችን እና አእምሮዋችን ሁሌ በዓብዩ ጌታ ፍቅር እና አገልግሎት የተሞላ ከሆነ ወዲያውኑ ስሜቶቻችን እና ገላችንም እንዲሁ በዓብዩ ጌታ አገልግሎት ላይ ይውላሉ፡፡ የብሀገቨድ ጊታም ሚስጢር ይኅው ነው፡፡ ይህንን ስልት እንዴት ሁሌ ሀሳባችንን እና አእምሮዋችንን በጌታ መመሰጥ እንደምንችል መማር ይኖርብናል፡፡ ይህም ሀሳብን እና አእምሮዋችንን ለ24 ሰዓት እንዴት ዓብዩ ጌታን ለማስታዋስ እንደምንችል ስልቱን በመፍጠር ነው፡፡ ይህም ስልት አንድ ሰውን ወደ መንፈሳዊው ዓለም እንዲሸጋገር ይረዳዋል፡፡ ወይም ይህንን ቁሳዊ ገላ ካለፈ በኋላ ወደ መንፈሳዊው ዓለም ለመሸጋገር ያበቃዋል፡፡ የአሁኑ ግዜ ሳይንቲስቶች ለብዙ ዓመታት ወደ ጨረቃ ለመድረስ ብዙ ሙከራ አድረገዋል፡፡ ቢሆንም ግን ወደ ሌላ ፕላኔቶች እንዴት የመሄድ ስልቱ ገና ግልፅ አልሆነላቸውም፡፡ ነገር ግን በዚሁ በብሀገቨድ ጊታ ውስጥ መልእክቱ ተላልፎልን ይገኛል፡፡ ለምሳሌ አንድ ሰው ለሀምሳ ዓመት ያህል ይኖራል እንበል ለሀምሳ ዓመት ያህልም ማንም ሰው በመንፈሳዊ እውቀት አልዳበረም እንበል ጥሩው መልእክት ግን ተገልፆልናል ለአስር ዓመትም ሆነ ለአምስት ዓመት አንድ ሰው በትሁትነት መንፈሳዊ አገልግሎቱን ቢያበረክት "ማዪ አርፒታ ማኖ ቡድሂር" (ብጊ፡ 8.7) ይህም የሚፈልገው መለማመድን ብቻ ነው፡፡ ይህን ልምምድ የትሁት አገልግሎትን ስርዓት በመከተል በቀላሉ ሊደረግ የሚችል ነው፡፡ ይህም በ"ሽራቫናም" ወይንም በማዳመጥ ይጀምራል፡፡ "ሽራቫናም" ይህም ከትሁት አገልግሎቶች ሁሉ በጣም ቀላሉ ስርዓት ነው፡፡

"ሽራቫናም ኪርታናም ቪሽኑ ስማራናም ፓዳ ሴቫናም አርቻናም ቫንዳናም ዳስያም ሳክያም አትማ ኒቬዳናም" (ሽብ፡ 7.5.23)

የትሁት አገልግሎት ዘጠኙ ስርዓቶች እነዚህ ናቸው፡፡ ከእነዚህም ሁሉ በጣም ቀላሉ "ሽራቫናም" ወይንም ማዳመጥ ነው፡፡